አቶ ጃዋር መሃመድ ፣ አቶ በቀለ ገርባ ፣ አቶ ሀምዛ አዳነ እና አቶ ደጀኔ ጣፋ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ጸረ ሽብርና ህገ መንግሥታዊ ወንጀሎች ችሎት በፃፉት ደብዳቤ ከዛሬ ጀምሮ በፍቃዳቸው ችሎት ላይ ለመቅረብ እንደማይችሉ ገለፁ።
በደብዳቤያቸው ላይ ፤ "መንግስት ከፊቱ ይጠብቀው ከነበረው ምርጫ ጠንካራ ተፎካካሪ ፓርቲዎችን ከወዲሁ ለማስወገድ አስቀድሞ ወጥኖ በነበረው ዕቅድ መሠረት የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳን ግድያ በማሳበብ እሥር ቤት ካጎረን እነሆ አንድ አመት ሆኖታል" ብለዋል። በዚህ ጊዜ ለሀገሪቱ የፍትህ ተቋም ክብር በመስጠት የቀረበብንን ክስ ህጋዊ በሆነ መንገድ ተከራክረን ንጽህናችንን ለማረጋገጥ በችሎት እየተገኘን በትዕግስት እና አርአያነት ባለው መልኩ ህግ አክባሪ ዜጎች መሆናችንን ለማስመስከር ሞክረናል ብለዋል። ይህንን ስናደርግ የነበረው በችሎቱ ለተሰየሙት ዳኞች ፣ ለሚያጅቡን ፖሊሶች እና ለምንገኝበት ማረሚያ ቤት ተገቢውን ክብር በመስጠት ሲሆን በመጨረሻም ፍርድ ቤቱ የሚሰጠውን ውሳኔ አስፈጻሚው የመንግስት አካል ተግባራዊ ያደርጋል በሚል ጽኑ እምነት ነበር ሲሉ ገልፀዋል። ነገር ግንበሂደቱ እንደተረዳነው ፍ/ቤቶች የሚሰጡት ውሳኔ በህገወጥ መንገድ እየተጣሰ በነፃ የተሰናበቱ ዜጎች በመንግስት ኃይሎች እየተጠለፉ ወደ ሌላ እስር ቤት ሲወሰዱ አንዳንዴም ደብዛቸው ሲጠፋ ተመልክተናል ብለዋል።
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
አስተያየቶች ለጥፍ (Atom)
ቻይና በአሜሪካ ባለስልጣናት ላይ ማዕቀብ እየጣለች ነው።
ቻይና በአሜሪካ ባለስልጣናት ላይ ማዕቀብ እየጣለች ነው። ቻይና በርከት ባሉ የአሜሪካ ባለሥልጣናት እና ተቋማት ላይ ማዕቀብ እየጣለች ትገኛለች። ሀገሪቱ ማዕቀብ እየጣለች የምትገኘው አሜሪካ በሆንግ ኮንግ ባለሥልጣናት ላይ ...
-
#FDREDefenseForce የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት በመሰረታዊ ውትድርና ያሰለጠናቸውን 2ኛ ዙር ምልምል ወታደሮች እያስመረቀ ይገኛል። ተመራቂዎቹ በቆይታቸው ወቅት ለውትድርና ሙያ ብቁ የሚያደርጋቸውን ...
-
ሰለሞን ቱፋ ለ ነሀስ 🥉 ሜዳሊያ ይወዳደራል ! የጃፓኑን ተጋጣሚው ሰርጅዮ ሱዙኪ በመርታት ወደ ሩብ ፍፃሜው ያለፈው ሰለሞን ቱፋ ደምሴ በቱኒዚያው ተፎካካሪው በነጥብ ልዩነት ቢሸነፍም በተሻለ ነጥብ ወደ ቀጣዩ ዙር በማለፍ...
-
አልፋ መረጃ 40 ሺህ ዜጎችን የመመለሱ ዘማቻ ተጀመረ። በሳውዲ ዐረቢያ እስር ቤቶች እየተሰቃዩ ያሉ ዜጎችን ከትላንት ሌሊት ጀምሮ መመለስ ተጀምሯል። የኢትዮጵያ አምባሳደር ሌንጮ ባቲ እስረኞችን ወደ ሀገር የመመለስ...


ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ